Telegram Group & Telegram Channel
የእኔ ታሪክ (በ አዲስ ምዕራፍ)
ቪቪያን እንደፃፈችው........

የሰው ልጅ ታሪክ መጨረሻ የለውም። ሞት መጨረሻ ነው ብዬ እንዳልደመደም ከሚያደርጉኝ ነገሮች አንዱ ልጅ ነው። የአባቴ ታሪክ እዚህ ላይ ያበቃ ቢመስልም በእኔ እና በአሌፍ ግን ነፍስ ዘርቶ ቀጥሏል። እንዲህ ሆነ.........ወደኋላ ተመልሳ ከአባቷ ጋ ያሳለፈችውን የመጨረሻ ቀን አስታወሰች።


ያቀፏት የሕዝቅኤል እጆች ድንገት ተንሸራተው ሲወድቁ የእርሷም ልብ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ብሎ ሲወድቅ ታወቃት። ለመናገር ቃላቶች አልነበሯትም አይኗ ብቻ በሚያፈሰው ውሃ ያወራል። ያ ሕይወቱን ሙሉ በመከራ ያሳለፈው ሕዝቅኤል ለዘለዓለም አልተነሳም። ከቁስሉ ሊያገግም ፣ ለብዙ አመት የተከደነው ጥርሱ ሊስቅ ፣ በእንባ ብዛት የሟሙ አይኖቹ እንደገና የተስፋ ጭላንጭል ሊያበሩ በነበረበት ቅፅበት ሕዝቅኤል ድንገት አመለጠ። ከእነሱ ከእናት እና አባቱ፣ ከእህቱ እና ከወንድሙ ጋ ተቀላቀለ....... ህይወት ፍትሃዊ አይደለችም። ያንን ሁሉ የስቃይ እና የመከራ አመታት ሲያሳልፍ ዞር ብሎ ያላየው ሞት...... ለደስታው በተቃረበ ሰዓት ግን ሊወስደው አሰፈሰፈ።


ማቲያስ የተደወለለትን ስልክ አናግሮ ከጨረሰ በኋላ አንድ ጋዜጣ እያነበበ የነበረ ሰው አጠገብ ሄዶ ተቀመጠ። የሰውዬውን ሁኔታ ከላይ እስከታች አጤነው....የሚያውቀው መስሎ ተሰማው ግን የት እንደሆነ ማስታወስ አልቻለም ለዛም ሊያናግረው ፈልጎ ጉሮሮውን ጠራረገ። እንዴት ዋሉ አባ.....? ሰውየው ጋዜጣቸውን ዝቅ አድርገው ወደጠራቸው ሰው ዞር አሉና ፈገግ አሉ። ምኔን አይተህ ነው አባ ያልከኝ ልጄ .......ፂምወትን አለ ቀለል ያሉ ሰው እንደሆኑ ከንግግራቸው ተረድቶ......ቀጠል አድርጎም እርሶስ ምኔን አይተው ነው ልጄ ያሉኝ አለ ጨዋታ ለመፍጠር ያክል.......እሳቸውም ወጣትነትን ብለው ፈገግ አሉ። ማቲያስ እባላለሁ አለ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋላቸው፤ ሰውየው ድንግጥ ብለው ማቲያስ አሉ የተዘረጋላቸውን እጅ እየጨበጡ። አወ የእርሶስ አለ ማቲያስ የፊታቸውን መቀየር እያጤነ። የእኔን ስም ነበር ማቲያስ ያልኩህ ማቲያስ እባላለሁ ..........የስማችን መመሳሰል ገርሞኝ ነውኮ መደንገጤ።


ወጣቱ ማቲያስ ወዲያው የሜሮን የቀድሞ ፍቅረኛ አእምሮው ላይ ብልጭ አለ። ጋሽ ሕዝቅኤል ጓደኛወት ነው? አብርሃምም?.....ሽማግሌው ደነገጠ ማነህ አንተ?..............መጀመሪያ ጥያቄዬን ይመልሱልኛ.... አወ ማን ነህ?......የሜሮን ልጅ.........በእድሜ ብዛት የማያረጀወሰ የሽማግሌው ማትያስ ፍቅር ስሟን ሲሰማ እንደገና አገረሸ። ወጣቱን አስተዋለው እውነትም እሷን ይመስላል ..........እኔኮ አመጣጤ ሕዝቅኤል መታመሙን ሰምቼ ነበር......አለ አሁንም ድንጋጤው እንደወረረው። ና ወደውስጥ ጋሽ ሕዝቅኤልንም እየው እማዬም አለች.........ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ።.......ሲገቡ ግን የሕዝቅኤል አይኖች ከሚወደው ጓደኛው ከማትያስም በቅፅበታት ቀድመው ተከድነዋል።


ሆስፒታሉ ሌላ ድባብ ሞልቶታል ቃል የሞላው ቃል አልባ እንባ ከየ አቅጣጫው ይፈሳል ማቲያስ በቁሙ ራደ። ሀዘን ሀዘን ብቻ ተነበበ። ሁሉም የምሬት እንባውን ያነባል......የአሌፍ ግን ቃልም አለው። ለዚህ ነው እንዳውቅህ ያደረግከው? ትተኸኝ ለመሄድ...አባ ለምን? እስከዛሬ ትናፍቀኝ አልነበረ? ስታገኘኝ ጥለኸኝ ለመሔድ ነበር?


ግን ሆነ ሕዝቅኤል ላይመለስ አይኖቹ ተከደኑ። የሚወዱትም ነፍሶች ላይጠገኑ ተሰበሩ። ስርዓተ ቀብሩም ራቢያም ራሷ በተገኘችበት ተፈፀመ።ራቢያ ለዚህ ሁሉ አመታት አፍና የያዘችውን የስቃይ እንባ በመቃብሩ ላይ ዘረገፈችው አልቅሳ አልቅሳ አልጠገበችም አትጠግብምም። አለመኖሩን ሳታይ አምና የነበረችው ራቢያ አይታ ስታረጋግጥ ግን ለመቀበል አልቻለችም አቃታት።


ኤልሳ ልትናገር ይቅርና መቆም አቅቷት ለቀብሩም በሰወች ተደግፋ ነበር የመጣችው። የመጨረሻ ቃሏ " ላልድን ሰበርከኝ አይደል?" የሚል ነበር ከዛ ቃል በኋላ ከ አፏ የወጣ አንድም ቃል የለም። የእሷም አንደበት ከ ህዝቅኤል ጋር ተቀበረ።


ቪቪያን ውስጧ ነው የሚያወራው አይኗ ደግሞ በእንባ ቃላቶቹን ያወጣል። ብቻ ግን ስትታይ ከማዘን አልፎ ሕመሟ ይጋባል ።
ጓደኛው ማቲያስ ቪቪያንን አይቷት ውስጧን አነበበው። እንደ ሕዝቅኤልም ሊጠብቃት ለራሱ ቃል ገባ።
ሁሉንም ሰው በአንድ ላይ የሰበረ ቀን.....

ይቀጥላል ........

@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot



tg-me.com/nibab_lehiwot/196
Create:
Last Update:

የእኔ ታሪክ (በ አዲስ ምዕራፍ)
ቪቪያን እንደፃፈችው........

የሰው ልጅ ታሪክ መጨረሻ የለውም። ሞት መጨረሻ ነው ብዬ እንዳልደመደም ከሚያደርጉኝ ነገሮች አንዱ ልጅ ነው። የአባቴ ታሪክ እዚህ ላይ ያበቃ ቢመስልም በእኔ እና በአሌፍ ግን ነፍስ ዘርቶ ቀጥሏል። እንዲህ ሆነ.........ወደኋላ ተመልሳ ከአባቷ ጋ ያሳለፈችውን የመጨረሻ ቀን አስታወሰች።


ያቀፏት የሕዝቅኤል እጆች ድንገት ተንሸራተው ሲወድቁ የእርሷም ልብ ላይ የሆነ ነገር ቁርጥ ብሎ ሲወድቅ ታወቃት። ለመናገር ቃላቶች አልነበሯትም አይኗ ብቻ በሚያፈሰው ውሃ ያወራል። ያ ሕይወቱን ሙሉ በመከራ ያሳለፈው ሕዝቅኤል ለዘለዓለም አልተነሳም። ከቁስሉ ሊያገግም ፣ ለብዙ አመት የተከደነው ጥርሱ ሊስቅ ፣ በእንባ ብዛት የሟሙ አይኖቹ እንደገና የተስፋ ጭላንጭል ሊያበሩ በነበረበት ቅፅበት ሕዝቅኤል ድንገት አመለጠ። ከእነሱ ከእናት እና አባቱ፣ ከእህቱ እና ከወንድሙ ጋ ተቀላቀለ....... ህይወት ፍትሃዊ አይደለችም። ያንን ሁሉ የስቃይ እና የመከራ አመታት ሲያሳልፍ ዞር ብሎ ያላየው ሞት...... ለደስታው በተቃረበ ሰዓት ግን ሊወስደው አሰፈሰፈ።


ማቲያስ የተደወለለትን ስልክ አናግሮ ከጨረሰ በኋላ አንድ ጋዜጣ እያነበበ የነበረ ሰው አጠገብ ሄዶ ተቀመጠ። የሰውዬውን ሁኔታ ከላይ እስከታች አጤነው....የሚያውቀው መስሎ ተሰማው ግን የት እንደሆነ ማስታወስ አልቻለም ለዛም ሊያናግረው ፈልጎ ጉሮሮውን ጠራረገ። እንዴት ዋሉ አባ.....? ሰውየው ጋዜጣቸውን ዝቅ አድርገው ወደጠራቸው ሰው ዞር አሉና ፈገግ አሉ። ምኔን አይተህ ነው አባ ያልከኝ ልጄ .......ፂምወትን አለ ቀለል ያሉ ሰው እንደሆኑ ከንግግራቸው ተረድቶ......ቀጠል አድርጎም እርሶስ ምኔን አይተው ነው ልጄ ያሉኝ አለ ጨዋታ ለመፍጠር ያክል.......እሳቸውም ወጣትነትን ብለው ፈገግ አሉ። ማቲያስ እባላለሁ አለ እጁን ለሰላምታ እየዘረጋላቸው፤ ሰውየው ድንግጥ ብለው ማቲያስ አሉ የተዘረጋላቸውን እጅ እየጨበጡ። አወ የእርሶስ አለ ማቲያስ የፊታቸውን መቀየር እያጤነ። የእኔን ስም ነበር ማቲያስ ያልኩህ ማቲያስ እባላለሁ ..........የስማችን መመሳሰል ገርሞኝ ነውኮ መደንገጤ።


ወጣቱ ማቲያስ ወዲያው የሜሮን የቀድሞ ፍቅረኛ አእምሮው ላይ ብልጭ አለ። ጋሽ ሕዝቅኤል ጓደኛወት ነው? አብርሃምም?.....ሽማግሌው ደነገጠ ማነህ አንተ?..............መጀመሪያ ጥያቄዬን ይመልሱልኛ.... አወ ማን ነህ?......የሜሮን ልጅ.........በእድሜ ብዛት የማያረጀወሰ የሽማግሌው ማትያስ ፍቅር ስሟን ሲሰማ እንደገና አገረሸ። ወጣቱን አስተዋለው እውነትም እሷን ይመስላል ..........እኔኮ አመጣጤ ሕዝቅኤል መታመሙን ሰምቼ ነበር......አለ አሁንም ድንጋጤው እንደወረረው። ና ወደውስጥ ጋሽ ሕዝቅኤልንም እየው እማዬም አለች.........ተያይዘው ወደውስጥ ገቡ።.......ሲገቡ ግን የሕዝቅኤል አይኖች ከሚወደው ጓደኛው ከማትያስም በቅፅበታት ቀድመው ተከድነዋል።


ሆስፒታሉ ሌላ ድባብ ሞልቶታል ቃል የሞላው ቃል አልባ እንባ ከየ አቅጣጫው ይፈሳል ማቲያስ በቁሙ ራደ። ሀዘን ሀዘን ብቻ ተነበበ። ሁሉም የምሬት እንባውን ያነባል......የአሌፍ ግን ቃልም አለው። ለዚህ ነው እንዳውቅህ ያደረግከው? ትተኸኝ ለመሄድ...አባ ለምን? እስከዛሬ ትናፍቀኝ አልነበረ? ስታገኘኝ ጥለኸኝ ለመሔድ ነበር?


ግን ሆነ ሕዝቅኤል ላይመለስ አይኖቹ ተከደኑ። የሚወዱትም ነፍሶች ላይጠገኑ ተሰበሩ። ስርዓተ ቀብሩም ራቢያም ራሷ በተገኘችበት ተፈፀመ።ራቢያ ለዚህ ሁሉ አመታት አፍና የያዘችውን የስቃይ እንባ በመቃብሩ ላይ ዘረገፈችው አልቅሳ አልቅሳ አልጠገበችም አትጠግብምም። አለመኖሩን ሳታይ አምና የነበረችው ራቢያ አይታ ስታረጋግጥ ግን ለመቀበል አልቻለችም አቃታት።


ኤልሳ ልትናገር ይቅርና መቆም አቅቷት ለቀብሩም በሰወች ተደግፋ ነበር የመጣችው። የመጨረሻ ቃሏ " ላልድን ሰበርከኝ አይደል?" የሚል ነበር ከዛ ቃል በኋላ ከ አፏ የወጣ አንድም ቃል የለም። የእሷም አንደበት ከ ህዝቅኤል ጋር ተቀበረ።


ቪቪያን ውስጧ ነው የሚያወራው አይኗ ደግሞ በእንባ ቃላቶቹን ያወጣል። ብቻ ግን ስትታይ ከማዘን አልፎ ሕመሟ ይጋባል ።
ጓደኛው ማቲያስ ቪቪያንን አይቷት ውስጧን አነበበው። እንደ ሕዝቅኤልም ሊጠብቃት ለራሱ ቃል ገባ።
ሁሉንም ሰው በአንድ ላይ የሰበረ ቀን.....

ይቀጥላል ........

@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot
@nibab_lehiwot

BY ሕይወትን - በገፅ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/nibab_lehiwot/196

View MORE
Open in Telegram


ሕይወትን በገፅ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Spiking bond yields driving sharp losses in tech stocks

A spike in interest rates since the start of the year has accelerated a rotation out of high-growth technology stocks and into value stocks poised to benefit from a reopening of the economy. The Nasdaq has fallen more than 10% over the past month as the Dow has soared to record highs, with a spike in the 10-year US Treasury yield acting as the main catalyst. It recently surged to a cycle high of more than 1.60% after starting the year below 1%. But according to Jim Paulsen, the Leuthold Group's chief investment strategist, rising interest rates do not represent a long-term threat to the stock market. Paulsen expects the 10-year yield to cross 2% by the end of the year. A spike in interest rates and its impact on the stock market depends on the economic backdrop, according to Paulsen. Rising interest rates amid a strengthening economy "may prove no challenge at all for stocks," Paulsen said.

How Does Bitcoin Work?

Bitcoin is built on a distributed digital record called a blockchain. As the name implies, blockchain is a linked body of data, made up of units called blocks that contain information about each and every transaction, including date and time, total value, buyer and seller, and a unique identifying code for each exchange. Entries are strung together in chronological order, creating a digital chain of blocks. “Once a block is added to the blockchain, it becomes accessible to anyone who wishes to view it, acting as a public ledger of cryptocurrency transactions,” says Stacey Harris, consultant for Pelicoin, a network of cryptocurrency ATMs. Blockchain is decentralized, which means it’s not controlled by any one organization. “It’s like a Google Doc that anyone can work on,” says Buchi Okoro, CEO and co-founder of African cryptocurrency exchange Quidax. “Nobody owns it, but anyone who has a link can contribute to it. And as different people update it, your copy also gets updated.”

ሕይወትን በገፅ from hk


Telegram ሕይወትን - በገፅ
FROM USA